የተጣሩ መረጃዎች

ምስሉ ወደ አማራ ክልል በአውሮፕላን ተጭነው የሚሄዱ ወታደሮችን አያሳይም

ከ50ሺህ በላይ ተከታዮች ያሉት አንድ የትዊተር ገፅ ወደ አማራ ክልል የሚሄዱ ወታደሮችን የጫነ አውሮፕላንን ያሳያል በማለት  አንድን ምስል አጋርቷል

ይህ ጽሁፍ እስከሚታተምበት ጊዜ ድረስ ፖስቱ​​​​ 61 ጊዜ ያህል ተጋርቶ እና ከ80 በላይ ግብረመልሶችን አግኝቶ ነበር።

ይሁን እንጂ ሀቅቼክ ምስሉን ወደ አማራ ክልል የሚሄዱ ወታደሮችን የጫነ አውሮፕላንን እንደማያሳይ አረጋግጧል። በዚህም የትዊተር ፖስቱ ሀሰት ተብሏል።

እ.አ.አ በየካቲት 2023 የኢትዮጵያ መንግስት  የክልል ልዩ ሀይሎችን እንዲበተኑ እና ወደ መከላከያ ሰራዊት፣ ወደ ፌደራል ፖሊስ ወይም ወደ ክልል መደበኛ ፖሊስ እንዲቀላቀሉ ወስኗል። ይህም በአማራ ክልል የሚገኘውን ፋኖ በመባል የሚጠራውን የታጠቀ ቡድን  ያበሳጨና ተቃውሞ ያስነሳ ነው ። ይህን ተከትሎ በፋኖ ታጣቂዎችና  በመንግስት ወታደሮች መካከል ብዙ ግጭቶች ተካሂደዋል።

እ.ኤ.አ. ነሀሴ 11 ቀን 2023 የወጡ ዘገባዎች እና የማህበራዊ ሚዲያ ጽሁፎች እንዳመላከቱት በዚህ ግጭት ሳቢያ በርካታ ጉዳቶች ተከስተዋል።

ምንም እንኳን መንግስት የአማራ ክልል ትላልቅ ከተሞችን መልሶ ቢቆጣጠርም አሁንም በኢትዮጵያ ሰራዊት እና በፋኖ ሚሊሻ ቡድኖች መካከል ያለው ግጭት ቀጥሏል።

በዚህ መነሻነት የኢትዮጵያ መንግስት ወታደሮች በአውሮፕላን ወደ አማራ ክልል እያጓጓዘ እና እያሰማራ እንደሆነ የሚገልጽ አንድ የኤክስ (ትዊተር) ፖስት ተመልክተናል። ፖስቱ አንድ ምስል አያይዞ ነበር የተጋራው። ይህ በኤክስ የተጋራው ምስል  የመከላክያ ወታደሮች በሄሊኮፕተር ወደ አማራ ክልል እየተወሰዱ ያሳያል በማለት የቀረበ ነው።

ይሁን እንጂ ምስሉ ከቆየ ቪድዮ ላይ ተቆርጦ የተወሰደና ዋናው ምስል በፌስቡክ ነሀሴ 2 ቀን 2021 በተሰራጨ ቪዲዮ ላይ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወታደሮች፣ ሎጅስቲክስ እና የጦር መሳሪያን ወደ ትግራይ አጓጉዟል ከሚል ፖስት ላይ የተወሰደ ነው።

ስለዚህ ሀቅቼክ  የኤክስ ፖስቱን ሀሰት ብሎታል።

የቆዩ የማኅበራዊ ሚዲያ መልዕክቶች ላይ አርትዖት መስራት ፤ አዲሱ የሀሰተኛ መረጃ ስርጭት ስልት

የፌደራሉ መንግስት የክልል ልዩ ሀይሎችን ትጥቅ በማስፈታት እንደፍላጎታቸው ወደመከላከያ ፤ ፌደራል እና የክልል ፖሊስ እንዲቀላቀሉ ውሳኔ ማሳለፉን ተከትሎ በአማራ ክልል ግጭት መከሰቱ ይታወሳል። ይህ በክልሉ የተከሰተው ግጭት ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ይበልጥ እየተባባሰ እና ጉዳት እያስከተለ መምጣቱን የሚያሳዩ ሪፖርቶች እየወጡ ይገኛሉ።

ይህን ተከትሎ አማራ ክልል በፌደራል መንግስት እና በፋኖ ታጣቂዎች መካከል የተካሄዱ የተለያዩ ግጭቶችን እና ጦርነቶችን እያስተናገደ ይገኛል። በክልሉ ባለው ግጭትም የሰው ልጅ ህይወት ሲጠፋ የተለያዩ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶችም እንደተካሄዱ የሚያሳዩ የተለያዩ ሪፖርቶች እየወጡ ይገኛሉ።         


በሰኔ ወር የፋኖ ታጣቂዎች ጎንደር እና ደብረታቦርን ጨምሮ በአማራ ክልል የሚገኙ ዋና ዋና ከተማዎችን ተቆጣጥረው እንደነበር ይታወሳል። ይህን ሁኔታ ተከትሎ በክልሉ የተከሰተው ችግር  ክልሉ ባለኝ አቅም ልገታው አልችልም በማለት የፌደራሉ መንግስት ጣልቃ እንዲገባ እና መፍትሄ እንዲሰጥ ጥሪ አቅርቧል። ከጥሪው በፊት በክልሉ የተወሰኑ አከባቢዎች ይንቀሳቀስ የኢፌድሪ መከላከያ ሰራዊት የክልሉን ጥሪ ተከትሎ በክልሉ በርካታ ቦታዎች ላይ ወታደሮቹን አሰማርቷል። በክልሉ የተከሰተውን ሁኔታ በዘላቂነት ለመቆጣጠር ያግዝ ዘንድ የኢፌድሪ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ በአማራ ክልል ላይ ተፈፃሚነት እንዲኖረው ማፅደቁ ይታወሳል።

የፌደራል መንግስት ሀይሎች መጀመሪያ አካባቢ ስኬታማ የነበሩ ሲሆን በፋኖ ታጥቂዎች ስር የነበሩ የተለያዩ ከተማዎችንም መልሶ መቆጣጠር ችለው ነበር። ይሁን እንጂ አሁንም በክልሉ ላለው ግጭት ዘላቂ መፍትሄ ማግኘት ያልተቻለ ሲሆን ይህም ተጨማሪ ግጭቶች እና አመፆች በክልሉ እንደሚቀጥሉ ተጨባጭ ስጋት አለ፡፡

ከአማራ ብሄር ተወላጆች እስር ጋር ተያይዞ እየወጡ ያሉ ሪፖርቶች 

የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ በአማራ ክልል ከታወጀበት ከሐምሌ 28 ፤ 2015 ዓ.ም ጊዜ ጀምሮ የፌደራሉ መንግስት የአማራ ብሄር ተወላጆችን ጨምሮ ፖለቲከኞችን ፤ ጋዜጠኞችን እና ተፅዕኖ ፈጣሪዎችን አስሯል።

ከእነዚህም መካከል የቀድሞው የአማራ ክልል ምክር ቤት እና የገዥው ፓርቲ ብልፅግና አባል የነበሩት አቶ ዮሃንስ ቧያለው እንዲሁም የአማራ ብሄራዊ ንቅናቄ (አብን) አመራር እና የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል የሆኑት አቶ ክርስትያን ታደለ ለእስር ከተዳረጉት ጥቂት የአማራ ብሄር ተወላጆች ውስጥ ይጠቀሳሉ። 

እንደ መንግስት ሚድያዎች የዜና ዘገባ ከሆነ የፌደራሉ መንግስት 764 የሚሆኑ በክልሉ ያለውን የትጥቅ እንቅስቃሴ ይደግፋሉ ያላቸውን ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ማዋሉን ይፋ አድርጓል።   


ይሁን እንጂ የተለያዩ የማህበራዊ ሚድያ ሪፖርቶች መንግስት የአማራ ብሄር ተወላጆችን ኢላማ አድርጎ አዲስ አበባን ጨምሮ በተለያዩ የሀገሪቱ ከተሞች በሚገኙ የእስራ ማቆያ ቦታዎች እንዳሰራቸው እየተናገሩ ይገኛሉ።

ከዚህ ጉዳይ ጋር ተያይዘው እየወጡ ያሉ የማህበራዊ ሚድያ ላይ ፖስቶች በመንግስት እስር ላይ የሚገኙ የአማራ ብሄር ተወላጆችን የሚያሳዩ ናቸው በመባል እየተሰራጩ ይገኛሉ።

ለምሳሌ ያክል በመስከረም 2 ፤ 2016 ዓ.ም አንድ የፌስቡክ ገፅ (ከስር ያለውን ስክሪን ሾት ይመልከቱ) አራት ምስሎችን በማያያዝ ምስሎቹ በመንግስት አማካኝነት ከአዲስ አበባ ወጣ ብላ በምትገኘው ቱሉ ዲምቱ ከተማ ውስጥ በእስር ላይ የሚገኙ የአማራ ብሄር ተወላጆችን እንደሚያሳይ ከሚገልፅ ፅሁፍ ጋር አጋርቶ ነበር። ከዚህ በተጨማሪም ይህ የፌስቡክ ፖስት በካምፕ ውስጥ የሚገኙ እስረኞች ተላላፊ በሆኑ በሽታዎች እየተጠቁ እንደሆነም ገልጿል።  


[የመግለጫ ፅሁፍ ፡ እነዚህ በቱሉ ዲምቱ ካምፕ በእስር ላይ የሚገኙ እና በተላልፊ በሽታዎች የተጠቁ የአማራ ክልል ተወላጆች ናቸው]

ይህ ፖስት ብዙዎች ጋር መድረስ የቻለ ሲሆን ብዙ ግብረመልሶችንም ማግኘት ችሎ ነበር። ነገር ግን ሀቅቼክ ከዚህ ጋር ተያይዞ በቂ መረጃዎችን ማግኘት ስላልቻለ የምስሎቹን እርግጠኛነት ማጣራት አልቻለም።

የቆዩ ፖስቶችን ኤዲት ማድረግ

በሌላ በኩል አንዳንድ የመንግስት ደጋፊ የሚመስሉ የማህበራዊ ሚድያ አካውንቶች የዚህን ፌስቡክ ፖስት እና ስክሪን ሾት በማጋራት ምስሎቹ ከአመት በፊት እንደተጋራ ገልፀው ከአማራ ብሄር ተወላጆች እስር ጋር የሚያገናኘው ምንም ነገር እንደሌለ በመናገር ሲያጋሩ ቆይተዋል።

እነዚህ ፖስቶች የመጡት ምስሎቹ ሀሰተኛ እና መንግስት አሁን ያሰራቸውን የአማራ ክልል ተወላጆች እንደማያሳዩ ለማሳየት ነው።


(የመግለጫ ጽሁፍ ፡ እነዚህ ፖስቶች የተሳሳተ መረጃን ለማስተላለፍ ሀሰተኛ እና የቆዩ ምስሎችን ተጠቅመዋል)

ከስር ካለው ፌስቡክ ፖስት ላይ የተወሰደው ምስል (ስክሪን ሾት) የቆየ የፌስቡክ ፖስት ላይ የተጨመረ  ሲሆን ይህን አወዛጋቢ ምስል ለመጀመሪያ ጊዜ የተጋራው እዚህ ላይ ነው ለማስባል ይህ የፌስቡክ ገፅ ተጠቅሞበታል።         

 
(የመግለጫ ፅሁፍ፡ የአዲስ አበባ ከተማ መስተዳድር ከመቶ በላይ ለሚሆኑ ጎዳና ተዳዳሪዎች የህክምና አገልግሎት ሰጥቷል)

ሀቅቼክ ምስሎቹ እና የፌስቡክ ላይ ልጥፎቹ ከአንድ አመት በፊት መጋራታቸውን ለማጣራት ጥረት አድርጓል። ሀቅቼክም ሰኔ 22 ፤ 2014 ዓ.ም የተጋራ አንድ የፌስቡክ ፖስት እነዚህን ምስሎች ከአማርኛ የመግለጫ ፅሁፍ ጋር አጋርቶት እንደነበረ ማስተዋል ችሏል።

ኤዲት ተደርጎ (ተቀይሮ) የነበረው የፌስቡክ ፖስት


ሀቅቼክ የቆየ ምስሎች ናቸው ተብሎ የተጋራበት የፌስቡክ ፖስት በቅርቡ የተቀየረ እንደሆነ እንዲሁም ምስሉም ከፅሁፉ ጋር አብሮ የተቀየረ መሆኑን አረጋግጧል።

ይህ የፌስቡክ ፖስት ለመጀመሪያ ጊዜ ሰኔ 22 ፤ 2014 ዓ.ም በኦሮሚኛ ፅሁፍ ተጋርቶ የነበረ ሲሆን በመግለጫውም አምስት ግድያ የተፈፀመባቸውን እና ታላቅ ስብዕና አላቸው ያላቸውን ሰዎች የጠቀሰበት ፖስት ሲሆን እነሱም ጆን ኤፍ ኬኔዲ ፤ ማርቲን ሉተር ኪንግ ፤ አብርሃም ሊንከን ፤ ማልኮም እና ሃጫሉ ሁንዴሳ ነበሩ።   

     
ይህ ፖስትም ሰኔ 22 ፤ 2012 ዓ.ም የተገደለውን ታዋቂውን የኦሮሚኛ ሙዚቃ አቀንቃኝ አርቲስት ሃጫሉ ሁንዴሳን ከሌሎቹ አራት ሰዎች ጋር ያወዳደረብት የኦሮሚኛ ፅሁፍ ነበር። በመጀመሪያ የተጋራው ፖስት አንድ ምስል ብቻ እንደነበረው ማየት ይቻላል ነገር ግን ምስሉ ኤዲት ተደርጎ ስለወጣ እና በሌሎቹ ምስሎች ስለተተካ ሀቅቼክ የመጀመሪያውን ምስል ማግኘት አልቻለም።  

(ይህ ስክሪን ሾት ፡ ኦሪጅናሉን እና በኦሮሚኛ ፅሁፍ ተጋርቶ የነበረውን የሚያሳየው የፌስቡክ ፖስት ነው) 

ይሁን እንጂ ይህ የፌስቡክ ፖስት መስከረም 2 ፤ 2016 ዓ.ም እንደተቀየረ ያሳያል የኦሮሚኛ ፅሁፉም በሌላ የአማርኛ ፅሁፍ እንዲሁም አንድ የነበረው ምስል በሌሎች አምስት ምስሎች ተቀይሯል።

የተቀየረው እና አዲሱ ፖስት የሚያሳየው ፅሁፍ የአዲስ አበባ ከተማ መስተዳድር ከመቶ ለሚበልጡ የጎዳና ላይ ነዋሪዎች ነዋሪዎች የህክምና አገልግሎት እየሰጠ ነው የሚል መግለጫ ነው።  

(መስከረም 2 ፤ 2016 ዓ.ም ላይ የመግለጫ ፅሁፉ እንደተቀየረ እና አምስት ምስሎች እንደተጨመረበት ያሳያል)  

በዚህ ምክንያት ሀቅቼክ ይህንን የፌስቡክ ፖስት ሐሰት ብሎታል። ይህ ፖስት ሆን ተብሎ እና ሰዎችን ለማሳስት እንደተቀየረ በግልፅ ማየት ይቻላል። 

ሀቅቼክ የማህበራዊ ሚድያ ተጠቃሚዎች ከእነዚህ አይነት አሳሳች የሆኑ የማህበራዊ ሚድያ ፖስቶች መጠንቀቅ እንዳለባቸው ያሳስባል።

በተለይም ፌስቡክ ከፈረንጆቹ 2013 ጀምሮ ተጠቃሚዎች የሚያጋርቱን መልዕክት ላይ የአርታዖት ስራ እንዲሰሩ፣ ተመልሰው እንዲያስተካክሉ የሚፈቅድ አማራጭ ይፋ ማድረጉ ተከትሎ ጥንቃቄ ሊደረግ ይገባል። ተጠቃሚዎችም መረጃዎች የተጋሩበትን ቀን ከማየት ባለፈ የፖስቱን ኤዲት ሂስትሪ(የተጋራውን መልዕክት የአርትዖት ታሪክ) ማረጋገጥ ይኖርባቸዋል።     

ምስሉ በቅርቡ በፍኖተ ሰላም የተፈፀመ የአየር ጥቃትን ያሳያል?

ከ40ሺህ በላይ ተከታዮች ያሉት አንድ የፌስቡክ ገፅ የኢትዮጵያ መንግስት በቅርቡ በፍኖተ ሰላም የአየር ላይ ጥቃት በመፈጸም ከሶስት አመት በታች ያሉ ህጻናትን ጨምሮ 270 ንፁሀን ዜጎችን ገድሏል በሚል ይህን  ምስል  በስፋት አጋርቷል

ይህ ጽሁፍ እስከሚታተምበት ጊዜ ድረስ ፖስቱ ​​​​ 7000 ጊዜ ያህል በመታየት  ከ 300 በላይ ግብረመልሶችን አግኝቷል።

የፌድራል መንግስት እና በአማራ ክልል  በፋኖ ሚሊሻ ቡድኖች መካከል ግጭት እንዳለ ይታወቃል። ይህ ግጭት የተፈጠረው መንግስት የክልሉ የልዩ ሃይሎች ትጥቅ ፈትተው ከሌሎች የጸጥታ አደረጃጀቶች  ማለትም መክላክያ፣ ፌደራል ፖሊስ ወይም የክልል ፖሊስ ተቋማት ጋር እንዲዋሃዱ ባዘዘ ጊዜ ነው።

በአማራ ክልል እነዚህ የታጠቁ ሚሊሻዎች በርካታ አካባቢዎች ከተቆጣጠሩ በኋላ፣ የኢትዮጵያ ፌደራል መንግስት በክልሉ  የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አውጇል።

እ.ኤ.አ. ነሀሴ 11 ቀን 2023 የወጡ ዘገባዎች እና የማህበራዊ ሚዲያ ጽሁፎች በአማራ ክልል በተከሰተው ግጭት በርካታ ጉዳቶች መከሰታቸውን ይጠቁማሉ።

መንግስት በፋኖ ታጣቂዎች ጋር ባደረገው የመልሶ ማጥቃት ዘመቻ ዋና ዋና ከተሞችን መልሶ መቆጣጠር ችሏል። ያም ሆኖ በክልሉ ግጭቶች እንደቀጠሉ መረጃዎች ያሳያሉ።

ይህ በፌስቡክ የተጋራው ፎቶ የኢትዮጵያ አየር ሃይል በአማራ ክልል ፍኖተ ሰላም በተባለ ቦታ ላይ ጥቃት አድርሶ 270 ንጹሃንን  እንደገደለ ለማሳየት የቀረበ ነው። ይህ መረጃ እውነት መሆኑን ለማረጋገጥ ሀቅቼክ የጉግል ተገላቢጦሽ ምስል መፈለጊያን በመጠቀም ምስሉን መርምሯል። በዚህም ምስሉ ከዚህ በፊት በፌስቡክ ላይ የተለጠፈው በሀምሌ 21 ቀን 2023 መሆኑን አረጋግጧል።

በወቅቱ የተጋራው ይህ የፌስቡክ ፖስት የአውሮፕላኖቹን ብቃት  እንደሚያሳይ ከሚገልፅ ፅሁፍ ጋር ተጋርቶ ነበር። 

ስለዚህ ሀቅቼክ  በፍኖተስላም  የድሮን ጥቃት እንደነበረ እና ሰዎች እንደሞቱ የወጡ ዜናዎች ቢኖሩም፤ ነገር ግን ይህ የፌስቡክ ፖስት የቆየ ምስልን በመጠቀሙ ምክንያት ሀሰት ብሎታል።

አለምን ያወዛገቡ አስር የሀሰተኛ መረጃ ዘመቻዎች እና ጉዳታቸው

በታሪክ አጋጣሚዎች ውዝግብ ለመፍጠር፣ የህብረተሰቡን አስተሳሰብ ለመቀየር፣ እንዲሁም ማህበራዊ እና ፖለቲካዊ አለመረጋጋትን ለመፍጠር በማሰብ ሀሰተኛ መረጃዎች ሆን ተብለው ይሰራጫሉ።

እስቲ በታሪክ አጋጣሚ የተሰራጩ ታዋቂ ሀሰተኛ መረጃዎች እና ዘመቻዎችን እንመልከት፦

  1. የጽዮን (አይሁድ) ሽማግሌዎች ሰነድ

ይህ ፅሁፍ ፀረ አይሁድ እና ሆን ተብሎ የተፈጠረ ሲሆን አይሁዶች አለምን ለመቆጣጠር እያሴሩ እንደሆነ የሚገልፅ ነው። ሰነዱ ለመጀመሪያ ጊዜ የታተመው በፈረንጆቹ 1903 በሩሲያ ውስጥ ነበር። ከዚያ በኋላ ይህ ፅሁፍ አሁን ድረስ ሰዎች አይሁዶች ላይ ጥላቻ እና አመፅ እንዲቀሰቅሱ እያደረገ ይገኛል። በዚህ መፅሀፍ ውስጥ ያለው መረጃ ሀሰተኛ መሆኑ ቢረጋገጥም አሁንም ድረስ በአንዳንድ የአለማችን ክፍሎች ዘንድ ይታመናል።

    2. ኤድስ በአሜሪካ እንደተፈጠረ

በፈረንጆቹ 1980ዎች የሶቭየት ህብረት ሀሰተኛ መረጃን ኦፕሬሽን ኢንፌክሽን (Operation INFEKTION) በሚል ዘመቻ አሜሪካ የኤች አይቪ ቫይረስን ለጦር መሳሪያነት በማሰብ በቤተሙከራ ፈጥራዋለች በማለት አሰራጭታ ነበር።

ይህ መረጃ በተለያዩ የሚድያ አማራጮች ላይ በስፋት መነገሩን ተከትሎ ኤች አይ ቪ ኤድስ ያለባቸው ሰዎች ላይ ትልቅ ጭንቀትና መገለል ፈጥሮ ነበር።

   3. የኢራቁ ሳዳም ሁሴን ጅምላ ጨራሹ መሳርያ

በፈረንጆቹ 2003 በኢራቅ ላይ በተደረገው ወረራ የአሜሪካ መንግስት እና አጋሮቿ ኢራቅ የጅምላ ጨራሽ መሳሪያዎች አላት ብለው ነበር። ይህ መረጃ ኢራቅን ለመውረር እና የሳዳም ሁሴን መንግስት ለመገርሰስ እንደ ምክንያት ቀርቦ ነበር። በኋላ ምንም አይት የጅምላ ጨራሽ መሳሪያዎች አለመገኘታቸውን ተከትሎ መረጃው በአለም አቀፍ ደረጃ ውግዘትን እና በመንግስት ላይ ያለን እምነት መሸርሸር እስከትሎአል።

  4. የራሽያ ጣልቃ ገብነት በ2016 የአሜሪካ ምርጫ

የአሜሪካ የደህንነት ተቋማቶች በ2016ቱ የአሜሪካ ፕሬዝደንታዊ ምርጫ የሩሲያ መንግስት የተለያዩ ዘመቻዎችን በማዘጋጀት በምርጫው ላይ ጣልቃ ገብቶ እንደነበር ይገልፃሉ። ይህም የተለያዩ የማህበራዊ ሚድያ ቦቶችን በመጠቀም ሀሰተኛ መረጃዎችን ማሰራጨት፣ የዲሞክራት ፓርቲ የኢሜል መልዕክቶችን በመጥለፍ ወዘተ ተሳትፏል ተብሏል። ይህ የራሽያ ጣልቃ ገብነት በምርጫ ሂደቱ ላይ የነበረውን እምነት ከመሸርሸሩም ባለፈ በአሜሪካ ውስጥ ፅንፈኝነት እንዲነግስ አድርጓል።

  5. የኮሮና ቫይረስን በተመለከተ የተሰራጩ የውሸት መረጃዎች

በኮቪድ 19 ወረርሽኝ ወቅት ስለ ቫይረሱ ምንጭ ፤ ስለክትባቱ እና ስለበሽታው አደገኛነት የሚመለከቱ የተለያዩ ሀሰተኛ መረጃዎች ሲሰራጩ ቆይተዋል። ይህም በማህበረሰቡ እና በህክምና ባለሙያዎች ዘንድ መወዛገብና አለመተማመን አስከትሏል። ታድያ እነዚህ ሀሰተኛመረጃዎች የኮሮና ቫይረስን ለመቆጣጠር የሚደረገውን ጥረት በእጅጉ ጎድቶታል።

  6. የራሽያው የቀድሞ ሰላይ መመረዝ

በፈረንጆቹ 2018 የቀድሞ የሩሲያ ሰላይ የነበረ ሰርጌ ስክሪፓል እና ሴት ልጁ ዩሊያ በእንግሊዝ ሳሊስበሪ ከተማ በነርቭ ጋዝ ተመርዘው ነበር። የእንግሊዝ መንግስት ለጥቃቱ የሩሲያን መንግስት የወነጀለ ሲሆን በተቃራኒው ሩሲያ ይህንን ጥቃት የፈፀመው የእንግሊዝ መንግስት መሆኑን ገልፆ ነበር።

  7. የካታሎንያ የነጻነት ሪፈረንደም

በፈረንጆቹ 2017 በስፔን የምትገኘው ካታሎኒያ የመገንጠል /ህዝበ ውሳኔ/ ጥያቄ  አቅርባ ነበር። የስፔን መንግስት ይህን የመገንጠል ጥያቄ /ህዝበ ውሳኔው/ ህገወጥ ነው በማለት ተናግሮ ነበር። ይህንን ተከትሎ በሁለቱም ወገኖች ሀሰተኛ መረጃዎች ሲሰራጩ ነበር። የመገንጠል ጥያቄ ደጋፊዎች መንግስት ሀሰተኛ መረጃን እያሰራጨ ነው ቢሉም በምላሹ የስፔን መንግስት እነዚህ የመገንጠል ጥያቄውን የሚደግፉ አካላት ሀስተኛ መረጃን እና አመፅን የሚቀሰቅሱ መረጃዎችን በማህበራዊ ሚድያ ላይ እያጋሩ ነው በማለት ገልፆ ነበር።

  8. የእንግሊዝ ከአውሮፓ ህብረት የመውጣት ህዝበ ውሳኔ

በፈረንጆቹ 2016 የእንግሊዝ መንግስት ከአውሮፓ ህብረት ለመውጣት ህዝበ ውሳኔን አካሂዶ ነበር። ይህንን ተከትሎ የተለያዩ ሀሰተኛ መረጃዎች ሲሰራጩ ቆይተዋል። ከነዚያም መካከል እንግሊዝ ህብረቱን ለቃ ከወጣች በሳምንት እስከ 350 ሚልዮን ፓውንድ ታተርፋለች የሚሉ መረጃዎች ሲሰራጩ ነበር። በሌላ በኩል እንግሊዝ ህብረቱን ለቃ ከወጣች የኢኮኖሚ ቀውስ ይከሰታል የሚሉ የተጋነኑ ዘመቻዎችም ነበሩ። የሀሰተኛ መረጃ አስተዋፅኦ ለዚህ ህዝበ ውሳኔ እስካሁን ድረስ ለቀጠሉ ውዝግቦች መንስኤ ሆኗል።

  9. የ2015ቱ የስደተኞች ቀውስ

በፈረንጆቹ 2015 ግሪክ ለስደተኞች ወደ አውሮፓ መግቢያ ዋነኛ ቦታ ሆና ነበር። ይህንን ከፍተኛ የሆነ የስደተኛ ቁጥርን ተከትሎ በስደተኞቹ ላይ ያነጣጠሩ ሀሰተኛ መረጃዎች ሲሰራጩ ነበር። ከዘመቻዎቹ መካከል የወንጀል ቁጥር ጨምሯል ፣ የሽብር ስጋቶች በርትተዋል የሚሉ ይገኙበታል።

  10. የዩክሬን ጦርነት

ከፈረንጆቹ 2014 ጀምሮ በሩሲያ እና ዩክሬን መካከል ግጭት እና የሀሰተኛ መረጃ ዘመቻዎችን ነበሩ።  የሩሲያ መገናኛ ብዙሃን ጣቢያዎች የዩክሬንን መንግስት ፋሽሽታዊ አገዛዝ ነው ሲሉ ነበር። እነዚህ ዘመቻዎች ግጭቱን ሲያባብሱ እና በዩክሬንና ራሽያ ህዝቦች መካከል የጥላቻ ስሜት ሲቀሰቅሱ ኖሯል።

ሀሰት፡ ምስሉ በአሁኑ ሰዓት በኢትዮጵያ ውስጥ የተከሰተውን ድርቅ አያሳይም

በየካቲት 16 ቀን 2015 ዓ.ም አንድ የትዊተር አካውንት በኦሮሚያ ክልል ቦረና ዞን ውስጥ የተከሰተውን ድርቅ ያሳያል በማለት አንድ ምስልን አያይዞ አጋርቶ ነበር። 

ይህ ፅሁፍ ለንባብ እስከበቃበት ጊዜ ድረስ ይህ የትዊተር ፖስት ከ2ሺህ በላይ እይታን ማግኘት የቻለ ሲሆን ከ50 ጊዜ በላይ ደግሞ መጋራት ችሏል።

ይሁን እንጂ ሀቅቼክ ምስሉ በአሁኑን ሰዓት በኢትዮጵያ ውስጥ ያለውን ድርቅ እንደማያሳይ በማረጋገጥ የትዊተር ፖስቱን ሀሰት ብሎታል።     

የተለያዩ ሪፖርቶች እንደሚያሳዩት ከሆነ በአሁኑ ሰዓት በተለያዩ የኦሮሚያ እና የሶማልያ ክልል አካባቢዎች ላይ ከባድ ድርቅ መከሰቱን ያሳያሉ።

ይህ ድርቅ በእነዚህ አካባቢዎች ለአምስት ተከታታይ አመታት ተከስቷል። ይሁን እንጂ በነዚህ አካባቢዎች ከተከሰቱት ድርቆች መካከል በቦረና የተከሰትው ድርቅ ከባዱ ነው።

በምስራቃዊ እና ደቡባዊ የኦሮሚያ ክልል አካባቢዎች በተለይም የቦረና አካባቢ ባለፉት አመታቶች ከባድ በሆነ ድርቅ የተጎዳ አካባቢ ነው። ከዚህ ድርቅ ጋር በተያያዘ በባለፈው አመት በሺዎች የሚቆጠሩ ህፃናት ፤ ሴቶች እና አረጋውያን በምግብ እጥረት እና በድርቁ ምክንያት የቀንድ ከብቶቻቸውን በማጣታቸው ምክንያት ለተለያዩ የጤና ችግሮች ተጋልጠው ነበር። 

በአሁኑ ሰዓት በእነዚህ አካባቢዎች የተከሰተው ድርቅ ከአየር ንብረት መለዋወጥ እንዲሁም እነዚህ አካባቢዎች  ዝናብ በማጣታቸው ምክንያት የተከሰተ ነው። 

ይህ ድርቅ ወደ 800ሺህ የሚጠጉ የዞኑ ነዋሪዎችን ለአስቸኳይ የምግብ እርዳታ ፈላጊዎች እንዲሆኑ ምክንያት ሆኗል።          

በኢትዮጵያ በምስራቁ ክፍል እና እንደ ቦረና ባሉ አካባቢዎች የሚኖሩ ነዋሪዎች ሙሉ በሙሉ እና በከፊል ማለት በሚቻል መልኩ በአርብቶ አደርነት የሚተዳደሩ ሲሆኑ ህልውናቸው በቀንድ ክብቶቻቸው ላይ የተመሰረተ ነው። 

ይህ ለአምስት ተከታታይ አመታት የጠፋው ዝናብ የቦረና እና አካባቢው ነዋሪዎችን ህይወት አበላሽቷል። 

በዚህ መረጃ ላይ ተመስርቶ ይህ የትዊተር አካውንት የሞቱ የቀንድ ከብቶችን ምስል በማያያዝ በአሁኑ ሰዓት በኦሮሚያ ክልል ቦረና ዞን የተከሰተውን ድርቅ ያሳያል በማለት አጋርቶት ነበር።     

ይሁን እንጂ ምስሉ የቆየ ሲሆን በአሁኑ ሰዓት በቦረና እና አካባቢው ያለውን ድርቅ አያሳይም።

ምስሉ ለመጀመሪያ ጊዜ በመጋቢት 9 ቀን 2014 ዓ.ም በአንድ የፌስቡክ ገፅ ላይ ተጋርቶ ነበር።

በወቅቱ የተጋራው ይህ የፌስቡክ ፖስት በኦሮሚያ የባሌ እና ቦረና አካባቢዎች በድርቅ መጠቃታቸውን እንደሚያሳይ ከሚገልፅ ፅሁፍ ጋር ተጋርቶ ነበር። 
ስለዚህ ሀቅቼክ በአሁኑ ወቅት በቦረና ዞን አስከፊ ድርቅ ቢኖርም ነገር ግን ይህ የትዊተር ፖስት የቆየ ምስልን በመጠቀሙ ምክንያት ሀሰት ብሎታል።

ሀሰት፡ ምስሉ በአቡነ አብርሃም መኖርያ ቤት ውስጥ የተገኘ የጦር መሳርያን አያሳይም

በጥር 28 ቀን 2015 ዓ.ም አንድ የትዊተር አካውንት ህገወጥ የጦር መሳርያዎች እና ጥይቶች በባህር ዳር ሀገረስብከት ሊቀጳጳስ እና የፓትርያርኩ ፅ/ቤት አመራር በሆኑት በአቶ አቡነ አብርሃም መኖርያ ቤት ውስጥ ተገኝተዋል በማለት ሶስት ምስሎችን አጋርቶ ነበር።

ይህ የትዊተር ፖስት በፖሊስ ፍተሻ ከአቡነ አብርሃም የመኖርያ ቤት ውስጥ አምስት ክላሽንኮቭ መሳርያዎች ከ235 ጥይት ጋር ተገኝቷል የሚል የመግለጫ ፅሁፍን አጋርቶ ነበር።  

ይህ ፅሁፍ ለንባብ እስከበቃበት ጊዜ ድረስ ይህ የትዊተር ፖስት ወደ አንድ መቶ ያህል ጊዜ መጋራት ችሎ የነበረ ሲሆን ወደ 20 ሺህ የሚጠጉ ሰዎች ተመልክተውታል።

ይሁን እንጂ ሀቅቼክ ምስሉን ተመልክቶ መረጃውን እንደማይደግፍ በማረጋገጥ ሀሰት ብሎታል። 

በጥር 14 ቀን 2015 ዓ.ም የቀድሞ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስትያን ሊቀ-ጳጳሳት ከቤተክርስትያኗ ሲኖዶስ እውቅና ውጭ የተለያዩ ጳጳሳትን ሾመዋል።

የደቡብ ምዕራብ ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ-ጳጳስ እና ሁለት ሌሎች ጳጳሳት አንድ ላይ በመሆን ወደ 26 የሚጠጉ ኤጲስ-ቆጶሳትን በተለያዩ የኦሮሚያ እና የደቡብ ኢትዮጵያ አካባቢዎች ሾመዋል። ከዚህም በተጨማሪ በአቡነ ሳዊሮስ አማካኝነት ወደ 70 የሚጠጉ ጳጳሳት በኦሮሚያ ክልል በሚገኙ የተለያዩ ደብሮች ላይ ተመድበው ነበር።

ከዚህ ሁኔታ በኋላ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስትያን ሲኖዶስ በዚህ ጉዳይ ላይ አስቸኳይ ስብሰባን በመጥራት ከቤተክርስትያኗ እውቅና ውጭ የተሾሙትን ጳጳሶች እና በሹመቱ ላይ የተሳተፉትን በሙሉ አውግዛለች።

ከዚህም በተጨማሪ የቤተክርስትያኗ ሲኖዶስ እነ አቡነ ሳዊሮስን እና ሌሎች ጳጳሳትን የቤተክርስትያኗን ቀኖና በመተላለፋቸው ምክንያት ከአባልነት አስወግዳቸዋለች።    

ከጥቂት ቀናት በኋላ ከቤትክርስትያኗ ተለይተው የወጡት ሊቀጳጳሳትም በበኩላቸው ወደ 12 የሚጠጉ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስትያን ሊቀጳጳሳትን በማውገዝ ከአባልነትም ማገዳቸውን አስታውቀው ነበር። 

የባህርዳር ሀገረስብከት እና የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤትክርስትያን ሊቀጳጳስ የሆኑት አቶ አቡነ አብርሃም ከቤትክርስትያኗ በተለዩት አዳዲሶቹ ሊቀጳጳሳት ከተገለሉት መካከል ናቸው።

በጥር 28 ቀን 2015 ዓ.ም የተጋራው ይህ የትዊተር ፖስት ህገወጥ የጦር መሳርያዎች እና ጥይቶች በባህር ዳር ሀገረስብከት ሊቀጳጳስ እና የፓትርያርኩ ፅ/ቤት አመራር በሆኑት በአቶ አቡነ አብርሃም መኖርያ ቤት ውስጥ ተገኝተዋል በማለት ሶስት ምስሎችን አጋርቶ ነበር። ከዚህም በተጨማሪ ይህ የትዊተር ፖስት በአቡነ አብርሃም የመኖርያ ቤት ውስጥ አምስት ክላሽንኮቭ መሳርያዎች ከ235 ጥይት ጋር ተገኝቷል የሚል የመግለጫ ፅሁፍን አጋርቶ ነበር።

ይሁን እንጂ ሀቅቼክ በዚህ የትዊተር አካውንት የተጋራውን መረጃ ተመልክቶ የተጋሩት ምስሎች የቆዩ እና መረጃውን የማይደግፉ እንደሆኑ አረጋግጧል። 

የመጀመርያው ምስል በአዲስ አበባ ቅንጡ የሆኑ ሆቴሎችን በሚያስተዋውቅ አንድ ድረ-ገፅ ላይ የተወሰደ ሲሆን እንደ ድረገፁ ከሆነ ምስሉ በአዲስ አበባ ቦሌ አካባቢ በሚገኝ እና ሸገር ሮያል የተሰኘ ሆቴል የውስጥ ክፍሎችን እንደሚያሳይ ተገልጿል።    

ሁለተኛው ምስል በመስከረም 20 ቀን 2013 ዓ.ም በአንድ የዜና ድረ-ገፅ ላይ ተጋርቶ የነበረ ሲሆን ከተጋራው ምስል ጋር ህንድ ከሩሲያ ጋር የ770,000 ክላሽንኮቭ መሳርያዎችን ለመግዛት የግዥ ስምምነት መፈፀሟን በሚያሳይ ፅሁፍ ስር አገኝቶታል።  

ሶስተኛው ምስል ደግሞ የአቡነ አብርሃም መሆኑ ይታወቃል። 

በዚህም ምክንያት ሀቅቼክ የትዊተር አካውንቱን ፖስት መርምሮ ሀሰት ብሎታል።

ሀሰት ፡ ምስሉ በጅማ ከተማ በኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያን ግለሰብ አመራር ቤት ውስጥ የተገኘን የጦር መሳርያ አያሳይም

በጥር 30 ቀን 2015 ዓ.ም ከ290ሺህ በላይ ተከታይ ያለው የፌስቡክ ገፅ “በጅማ ከተማ በአንድ የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያን መኖርያ ቤት ውስጥ የተገኘ የጦር መሳርያ።” በማለት ሶስት ምስሎችን በማያያዝ አጋርቶ ነበር። 


የመጀመርያው ምስል የተለያዩ ጠመንጃዎችን የሚያሳይ ሲሆን ሁለተኛው ምስል የጥይት እና የጦር መሳርያ ምስሎችን ያሳያል። ሶስተኛው ምስል ደግሞ የጦር መሳርያ የተገኘበትን ግለሰብ ምስል ያሳያል በማለት አጋርቶት ነበር። 

ከዚህም በተጨማሪ  ይህ የፌስቡክ ፖስት በምስሉ ላይ የተመለከተው ግለሰብ “በጅማ የማህበረ ቅዱሳን ማዕከል ሰብሳቢ እና የደብተራ መድሃንያለም ቤተክርስትያን ሰበካ ጉባኤ ምክትል ሊቀመንበር ነው።” የሚል የመግለጫ ፅሁፍን አብሮ አያይዟል።

ይህ የፌስቡክ ፖስት በብዙ ስዎች ዘንድ ተጋርቶ የነበረ ሲሆን ከ400 በላይ ግብረ መልሶችን ማግኘት ችሏል። 

ይሁን እንጂ ምስሎቹ የቆዩ ሲሆኑ በፌስቡክ ገፁ የቀረበውን መረጃ እንደማይደግፉ ሀቅቼክ ማረጋገጥ ችሏል።

በዚህም ምክንያት ሀቅቼክ መረጃውን ሀሰት ብሎታል።    

በጥር 14 ቀን 2015 ዓ.ም የቀድሞ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስትያን ሊቀ-ጳጳሳት ከቤተክርስትያኗ ሲኖዶስ እውቅና ውጭ የተለያዩ ጳጳሳትን ሾመዋል።

የደቡብ ምዕራብ ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ-ጳጳስ እና ሁለት ሌሎች ጳጳሳት አንድ ላይ በመሆን ወደ 26 የሚጠጉ ኤጲስ-ቆጶሳትን በተለያዩ የኦሮሚያ እና የደቡብ ኢትዮጵያ አካባቢዎች ሾመዋል። ከዚህም በተጨማሪ በአቡነ ሳዊሮስ አማካኝነት ወደ 70 የሚጠጉ ጳጳሳት በኦሮሚያ ክልል በሚገኙ የተለያዩ ደብሮች ላይ ተመድበው ነበር።

ከዚህ ሁኔታ በኋላ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስትያን ሲኖዶስ በዚህ ጉዳይ ላይ አስቸኳይ ስብሰባን በመጥራት ከቤተክርስትያኗ እውቅና ውጭ የተሾሙትን ጳጳሶች እና በሹመቱ ላይ የተሳተፉትን በሙሉ አውግዛለች።

ከዚህም በተጨማሪ የቤተክርስትያኗ ሲኖዶስ እነ አቡነ ሳዊሮስን እና ሌሎች ጳጳሳትን የቤተክርስትያኗን ቀኖና በመተላለፋቸው ምክንያት ከአባልነት አስወግዳቸዋለች።    

ከጥቂት ቀናት በኋላ ከቤትክርስትያኗ ተለይተው የወጡት ሊቀጳጳሳትም በበኩላቸው ወደ 12 የሚጠጉ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስትያን ሊቀጳጳሳትን በማውገዝ ከአባልነትም ማገዳቸውን አስታውቀው ነበር። 

በዚህ መረጃ ላይ በመመስረት በጥር 30 ቀን 2015 ዓ.ም አንድ የፌስቡክ ፖስት ሶስት ምስሎችን በማያያዝ “በጅማ የማህበረ ቅዱሳን ማዕከል ሰብሳቢ እና የደብተራ መድሃንያለም ቤተክርስትያን ሰበካ ጉባኤ ምክትል ሊቀመንበር በሆኑ ግለሰብ መኖርያ ቤት ውስጥ የጦር መሳርያ ተገኘ” በማለት አጋርቶ ነበር። 

የመጀመርያዎቹ ሁለት ምስሎች እንደ ማስረጃነት የተለያዩ የጠመንጃ እና የጥይት ምስሎችን የሚያሳዩ ሲሆን ሶስተኛው ደግሞ የግለሰቡን ምስል ያሳያል። 

ጠመንጃዎች የሚታዩበት የመጀመርያው ምስል በጥቅምት 19 ቀን 2012 ዓ.ም በቢቢሲ የአፋን ኦሮሞ ቋንቋ ላይ የኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን የተለያዩ የጦር መሳርያ መያዙን በሚገልፅ ፅሁፍ ስር ተጋርቶ ተገኝቷል።       

ሊንክ

ሁለተኛው ምስል ደግሞ በመስከረም 27 ቀን 2014 ዓ.ም በአንድ የሀገር ውስጥ የዜና ሚድያ ላይ ከተጋራ ፅሁፍ ላይ የተወሰደ ነው። በዜናው ላይም በአዲስ አበባ ከተማ አዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ የተለያዩ የጦር መሳርያ በቁጥጥር ስር መዋላቸውን እደሚያሳይ ይገልፃል።   

ሊንክ
በዚህም ምክንያት ሀቅቼክ የፌስቡክ ፖስቱን ሀሰት ብሎታል።

ሀሰት፡ ምስሉ በሻሸመኔ የኦርቶዶክስ ቤትክርስትያን ቅጥር ግቢ ውስጥ የተገኘ የጦር መሳርያን አያሳይም

ከ39ሺህ በላይ ተከታይ ያለው የፌስቡክ ገፅ “ይህ በሻሸመኔ ቤተ እምነት ቅጥር ግቢ ውስጥ በፍተሻ የተገኘ ነው።” የሚል ፅሁፍን በማያያዝ አንድ ምስል አጋርቶ ነበር። 

ይህ ፅሁፍ ለንባብ እስከበቃበት ጊዜ ድረስ ይህ የፌስቡክ ፖስት ከ13 ጊዜ በላይ መጋራት ችሎ ነበር።

ይሁን እንጂ ሀቅቼክ ምስሉ የቆየ እና ከዚህ መረጃ ጋር ምንም ግንኙነት እንደሌለው አረጋግጧል። 


ስለዚህም ሀቅቼክ ይህን የፌስቡክ ፖስት ሀሰት ብሎታል።   

በጥር 14 ቀን 2015 ዓ.ም የቀድሞ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስትያን ሊቀ-ጳጳሳት ከቤተክርስትያኗ ሲኖዶስ እውቅና ውጭ የተለያዩ ጳጳሳትን ሾመዋል።

የደቡብ ምዕራብ ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ-ጳጳስ እና ሁለት ሌሎች ጳጳሳት አንድ ላይ በመሆን ወደ 26 የሚጠጉ ኤጲስ-ቆጶሳትን በተለያዩ የኦሮሚያ እና የደቡብ ኢትዮጵያ አካባቢዎች ሾመዋል። ከዚህም በተጨማሪ በአቡነ ሳዊሮስ አማካኝነት ወደ 70 የሚጠጉ ጳጳሳት በኦሮሚያ ክልል በሚገኙ የተለያዩ ደብሮች ላይ ተመድበው ነበር።

ከዚህ ሁኔታ በኋላ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስትያን ሲኖዶስ በዚህ ጉዳይ ላይ አስቸኳይ ስብሰባን በመጥራት ከቤተክርስትያኗ እውቅና ውጭ የተሾሙትን ጳጳሶች እና በሹመቱ ላይ የተሳተፉትን በሙሉ አውግዛለች።

ከዚህም በተጨማሪ የቤተክርስትያኗ ሲኖዶስ እነ አቡነ ሳዊሮስን እና ሌሎች ጳጳሳትን የቤተክርስትያኗን ቀኖና በመተላለፋቸው ምክንያት ከአባልነት አስወግዳቸዋለች።    

ከጥቂት ቀናት በኋላ ከቤትክርስትያኗ ተለይተው የወጡት ሊቀጳጳሳትም በበኩላቸው ወደ 12 የሚጠጉ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስትያን ሊቀጳጳሳትን በማውገዝ ከአባልነትም ማገዳቸውን አስታውቀው ነበር። 

ከቤትክርስትያኗ ተለይተው የወጡት ሊቀጳጳሳት መሪ የሆኑት አቡነ ሳዊሮስ አቡን ጳውሎስን የምዕራብ አርሲ ሀገረስብከት በሻሸመኔ ከተማ አመራር አድርገው መሾማቸው ይታወቃል። አዲስ የተሾሙት ጳጳስ ወደ ሻሸመኔ ከተማ ለመግባት መጓዛቸውን ተከትሎ በከተማዋ ከፍተኛ ውጥረት ነግሶ ቆይቷል። 

እንደተለያዩ የዜና ሪፖርቶች ከሆነ በከተማዋ በተከሰተው ግጭት ወደ ሶስት የሚሆኑ ሰዎች መሞታቸው ተዘግቧል።  

ይህ የፌስቡክ ፖስትም በዚህ መረጃ ላይ ተመስርቶ የተጋራ ነው።

ሀቅቼክ መረጃውን ይደግፋሉ የተባሉትን ምስሎች ለማጣራት በደረገው ጥረት ምስሎቹ የቆዩ እና ከሁለት አመት በፊት ተጋርተው የነበሩ መሆናቸውን አረጋግጧል። 

ምስሉ ለመጀመርያ ጊዜ በመጋቢት 6 ቀን 2013 ዓ.ም በኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን የፌስቡክ ገፅ ላይ “የፌደራል ፖሊስ በሲዳማ ከተማ በግለሰብ መኖሪያ ቤት ውስጥ ተከማችቶ የነበረ የጦር መሳርያ በቁጥጥር ስር ውሏል።” በሚል መግለጫ ተጋርቶ ነበር። 

በዚህም ምክንያት ሀቅቼክ የፌስቡክ ፖስቱን ሀሰት ብሎታል። 

ሀሰት፡ ምስሉ በቅርቡ በአማራ ክልል አጣዬ ከተማ የተከሰተውን ግጭት አያሳይም

ከሰሞኑ በአጣዬ እና አካባቢው ከተከሰተው ግጭት ጋር ተያይዞ የሚቃጠሉ ቤቶችን የሚያሳዩ ምስሎች በማህበራዊ ሚድያው ላይ በስፋት ሲዘዋወሩ ቆይተዋል።

በጥር 16 ቀን 2015 ዓ.ም ከ5ሺህ በላይ ተከታይ ያለው የፌስቡክ ገፅ ከሰሞኑ በአማራ ክልል አጣዬ ከተማ በተከሰተው ግጭት የሚቃጠሉ ቤቶች የሚያሳይ ምስል በሚል መግለጫ ስር አንድ ምስል አጋርቶ ነበር።


ይህ ምስል ከሌሎች ሁለት ምስሎች ጋር በመሆን ሲጋራ የቆየ ሲሆን ከሁለት ሰዓታት በኋላ በአጣዬ ከተማ ከተከሰተው ግጭት ጋር በማያያዝ ከ5ሺህ በላይ ተከታይ ባለው አንድ የፌስቡክ ገፅ ላይ ተጋርቷል።

ይሁን እንጂ ሀቅቼክ ምስሉ ለመጀመርያ ጊዜ ከሶስት አመት በፊት በአንደ የፌስቡክ ገፅ ላይ ተጋርቶ የነበረ እንደሆነ እና አሁን በአጣዬ እና አካባቢው ከተከሰተው ግጭት ጋር እንደማይገናኝ አረጋግጦ የፌስቡክ ፖስቱን ሀሰት ብሎታል።

ሊንክ

ሊንክ

ከ2011 ዓ.ም ጀምሮ በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ እና የኦሮሞ ልዩ ዞኖች እንዲሁም አጎራባች አካባቢዎች ላይ ተከታታይ የሆነ ግጭት እና ግድያዎች ተፈፅመዋል። በጥቅምት 2011 ዓ.ም የወጣ አንድ ሪፖርት እንደሚያሳየው ከሆነ በጊዜው በአካባቢው በተከሰተው ግጭት ሶስት ሰዎች እንደሞቱ ገልጿል።

ከሁለት አመታት በኋላ በ2013 ዓ.ም በአማራ ክልል የኦሮሞ ልዩ ዞን ቦታዎች በተለይም በአጣዬ ከተማ ላይ ከባድ ግጭቶች ተከስተው ነበር።   

ግጭቱ ለሁለት ወራት ያክል ቆይቶ የነበረ ሲሆን በመቶዎች የሚቆጠሩ ንፁሀን ሰዎች ሲሞቱ በግጭቱ የቆሰሉም አሉ። በዚህ ግጭት ምክንያት በመጋቢት እና ሚያዝያ 2011 ዓ.ም ላይ ከ3 መቶ ሺህ በላይ ሰዎች ሲፈናቀሉ ከ3000 በላይ ቤቶች በቃጠሎ ምክንያት ወድመዋል።    

አንድ አራተኛ የሚሆነው የአጣየ ከተማ ክፍል በዚህ ግጭት ምክንያት ወድሟል። ይህ ግጭት ካስከተለው ጉዳት በኋላ የአማራ ክልል መንግስት ለመልሶ ግንባታ እና መልሶ ማቋቋሚያ የሚሆን ወደ 1.5 ቢልዮን ብር እንደሚያስፈልገው ገልጾ ነበር።  

በሚያዝያ ወር 2012 ዓ.ም ላይ በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ እና የኦሮሞ ልዩ ዞን አካባቢዎች ላይ ግጭቶች ተከስተው የነበረ ሲሆን ይህ ግጭት ለብዙ ሰዎች ህይወት መጥፋት ምክንያት ሆኗል።

ከሰሞኑ በሰሜን ሸዋ ዞን እና የኦሮሞ ልዩ ዞን በሚገኙት የአጣዬ እና የጀውሃ ከተሞች አካባቢ ግጭት መከሰቱን የተለያዩ የማህበራዊ ሚድያ ሪፖርቶች ያሳያሉ። 

ይህ መረጃ ላይ መሰረት በማድረግ ምስሉ በአጣዬ ከተማ የተፈፀመ ነው በማለት በተለያዩ የፌስቡክ ገፆች ላይ ሲዘዋወር ቆይቷል።


ይህ ምስል በጥር 16 ቀን 2015 ዓ.ም ላይ በሁለት የፌስቡክ ገፆች ላይ የተጋራ ሲሆን ሁለቱም የፌስቡክ ገፆች እያንዳንዳቸው ከ5ሺህ በላይ ተከታዮች አሏቸው።  

ይሁን እንጂ ሀቅቼክ ምስሉ የቆየ እና ከሰሞኑ በአጣዬ እና አካባቢው ከተፈጠረው ግጭት ጋር የሚያያዝ እንዳልሆነ ማረጋገጥ ችሏል።

ምስሉ ከሶስት አመት በፊት ሚያዝያ ወር 2011 ዓ.ም ላይ በአንድ የፌስቡክ ገፅ ላይ ተጋርቶ ነበር። ከምስሉ ጋር ያለው ፅሁፍ በወቅቱ በአጣዬ ከተማ በእሳት ቃጠሎ የተጠቃ ቤተክርስትያን እንደሚያሳይ ይገልፃል። ስለዚህ ሀቅቼክ መረጃውን አጣርቶ ሀሰት ብሎታል።

ሀሰት፡ ይህ ቪድዮ በወሎ በተከሰተው ግጭት የተቃጠለ የኦሮሞ ብሄር ተወላጅ ቤቶችን አያሳይም

በጥር 15 ቀን 2015 ዓ.ም ላይ ከ6ሺህ በላይ ተከታዮች ያሉት የፌስቡክ ገፅ “በአማራ ክልል የኦሮሚያ ልዩ ዞን ውስጥ የሚኖሩ የኦሮሞ ብሄር ተወላጆች ቤቶች እየተቃጠሉ ነው።” በማለት አንድ ቪድዮን አጋርቶ ነበር።


ከዚህ በተጨማሪም ይህ የፌስቡክ ገፅ በአካባቢው ያሉ የታጠቁ ሚሊሽያዎች የኦሮሞ ብሄር ተወላጆችን ንብረት እየዘረፉ እና እየገደሉ ነው በማለት መረጃን አጋርቷል።  
 

ይሁን እንጂ ሀቅቼክ ይህ የፌስቡክ ገፅ በቪድዮው ውስጥ የተጠቀመው ምስል የቆየ እንደሆነ እና መረጃውን እንደማይደግፍ አረጋግጦ ሀሰት ብሎታል።

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን እና በአጎራባች የኦሮሞ ልዩ ዞን በሆኑ አካባቢዎች የእርስ በርስ ግጭቶች በተደጋጋሚ እየተፈጠሩ ይገኛሉ።  

እንደ አንድ አንድ የማህበራዊ ሚድያ መረጃዎች ከሆነ ከሰሞኑ በነዚህ አካባቢዎች ግጭቶች ተከስተዋል።  

በጥር 16 ቀን 2015 ዓ.ም ኦሮሞ ነፃነት ግንባር (ኦነግ) ባወጣው መግለጫ በአማራ ክልል የኦሮሞ ልዩ ዞን አካባቢዎች በአማራ ክልል ታጣቂዎች አማካኝነት የተቀናጀ ጥቃት በኦሮሞ ብሄር ተወላጆች ላይ ተፈፅሟል በማለት ገልጿል።   

ከዚህ በተጨማሪም በመግለጫው ላይ የክልሉ የፀጥታ ሀይሎች እና የአካባቢው ሚሊሽያዎች በጥር 13 ቀን 2015 ዓ.ም ላይ በነዋሪዎች ላይ ጥቃት እንዳደረሱ ፤ ቤቶችን እንዳቃጠሉ እና ንብረቶችን እንደዘረፉ ገልጿል። 

ከዚህ በተጨማሪም የኦሮሞ ነፃ አውጭ ግንባር (ኦነግ) በግጭቱ ከ65 በላይ ንጹሀን መሞታቸውን በመግለጫው ላይ አንስቷል።  

ይህ የፌስቡክ ፖስትም የሚቃጠሉ ቤቶችን የሚያሳይ የምስል ቪድዮ ያጋራው በዚህ ሀሳብ ላይ መሰረት አድርጎ ነው።


ይሁን እንጂ ከቪድዮው ማየት እንደሚቻለው ምስሎችን ገጣጥሞ በመጠቀም የተፈጠረ ነው።     

ነገር ግን በቪድዮው ውስጥ ያለው ምስል ከዚህ በፊት በታኅሣሥ 14 ቀን  2013 ዓ.ም ከተጋራ ፅሁፍ ላይ የተወሰደ ነው።  

ሊንክከዚህ ፅሁፍ ጋር የተጋራው ምስል በቤንሻንጉል ክልል መተከል ዞን የሚኖሩ ብዙ ንፁሃን እንደተገደሉ በሚያሳይ ሪፖርት ስር ተጋርቷል።

ሀቅቼክ በዚህ የፌስቡክ ገፅ አማካኛነት መረጃውን ለመደገፍ የተጋራው ምስል የቆየ እና ከዚህ መረጃ ጋር የማይገናኝ መሆኑ በማረጋገጥ ሀሰት ብሎታል። 

Exit mobile version