ምስሉ በኢትዮጵያ አየር ሃይል የህወሃት ሃይል ላይ አርምጃ መወሰዱን ያሳያል?

ከ215,000 በላይ ተከታይ ያለው የፌስቡክ ገፅ ነሃሴ 5 2013 ዓ.ም ባጋራው  ልጥፍ ላይ መረጃውን “ሰበር ዜና” በማለት ያጋራ ሲሆን ሙሉ ትስሁፉም “በአማራ ክልል ልዩ ስሙ ገረገራ ትምሕርት ቤት ውስጥ በድብቅ ካንፕ ሰርቶ የመሽገው “የጁንታ ሐይል” ጥቃት ከመፈፀሙ በፊት በአየር ሐይላችን በተወስደ ኦፕሬሽን ሙሉ ለሙሉ ለመደምሰስ ተችሏል።’’ ሲል ይነበባል። በልጥፉ የተጠቀሰችው ገርገራ ከተማ በአማራ ክልል ሰሜን ወሎ ዞን ከላሊበላ 73.5 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የምትገኘው ከተማ ናት።

በመሆኑ ምስሎቹ ከጉዳዩ ጋር ምንም ግንኙነት የሌላቸው ሰለሆኑ ሀቅቼክ መረጃውን ሀሰት ብሎታል።

ይህ ልጥፍ ከህዳር 2013 ጀምሮ በኢትዮጵያ ፌደራል መንግስት እና በትግራይ ህዝብ ነፃ አውጪ ግንባር (ህወሓት) ጦር መካከል እየተካሄደ ያለውን ግጭት ተከትሎ በማህበራዊ ሚዲያ እየተዘዋወሩ ከነበሩት መካከል አንዱ ነው። ጦርነቱ ከተጀመረ ከሶስት ሳምንት በኋላ የፌደራል መንግስት የክልሉን ዋና ከተማ መቀሌን እና አብዛኛዎቹን የክልሉን ክፍሎች ተቆጣጥሯል።

ይሁን አንጂ ጦርነቱ ከተጀመረ ከስምንት ወራት በኋላ የፌዴራሉ መንግሥት ወታደሮቹን ከክልሉ ለማውጣት ወስኛለው በማለት የአንድ ወገን ሰብዓዊ የተኩስ አቁም አዋጅ ማወጁ ተሰምቷል። ይህን ተከትሎ የቀድሞው የክልሉ እና የህወሓት አመራሮች የኢትዮጵያ ሰራዊት ከክልሉ መውጣቱ ተከትሎ  ሰኔ 21 ቀን 2013 የክልሉን ዋና ከተማ እና አብዛኞቹን የክልል ግዛቶች መልሰው ተቆጣጠሩ።

የህወሓት-ሀይሎች ከ መካከለኛው የትግራይ ክፍል እየወጡ ወደ ደቡብ እና ደቡብ ምስራቅ መገስገስ በመጀመራቸው ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ትግራይን ፣ አማራ እና አፋር ክልልን በሚዋሰኑ የድንበር አካባቢዎች ግጭቶች መከሰታቸው ተዘግቧል። ሀምሌ 29 በአማራ ክልላዊ መንግስት ሰሜን ወሎ ዞን የላሊበላ ከተማን የህወሓት ሀይሎች  መቆጣጠራቸው ተዘግቧል። ያንን ተከትሎ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት ነሐሴ 4 ኢትዮጵያውያን በህወሓት ኃይሎች ላይ በሚደረገው ዘመቻ ላይ እንዲሳተፉ ጥሪ አቅርቧል። በአማራ ክልል የአየር ኃይሉ በህወሓት ጦር ላይ ጥቃት ፈፀመ የሚለው የፌስቡክ ጽሑፍ በእነዚህ ሁኔታዎች ወቅት ተጋርቷል።

ሃቅቼክ ሪቨርስ ኢሜጅ በተባለ የምስል ማጣሪያ ገፅ ምስሉን ፈልጎ፤  ምስሉ ለመጀመሪያ ጊዜ የተለጠፈው ጥር 5 2012 መሆኑን አረጋግጧል። ምስሉ የተወሰደው በወቅቱ በባርሴሎና አቅራቢያ በሰሜን ምስራቅ ስፔን በሚገኝ የፔትሮኬሚካል ፋብሪካ ላይ ከተከሰተ ፍንዳታ ላይ ነው።

የመጀመሪያው ምስል

መንግስት በህወሓት ሀይሎች ላይ ጥቃት መጀመሩን የሚገልጹ ዘገባዎች ቢኖሩም ፣ ሃቅቼክ ምስሉ በገረገራ በህወሓት ሀይሎች  ላይ የተፈጸመ ጥቃት አለመሆኑን አረጋግጧል። ስለሆነም ምስሉ ከጉዳዩ ጋር  ምንም ግንኙነት የሌለው በመሆኑ ሀቅቼክ የፌስቡክ ልጥፉን ሀሰት ብሎታል።  

Exit mobile version