አምስቱ የአፍሪካ ሀገሮች ግማሽ ያህል የሚሆነውን የአፍሪካ የሀገር ውስጥ ምርት ይሸፍናሉ?

ከሰሞኑ በአንድ የx ወይም በቀድሞ ስሙ ትዊተር ላይ የተጋራ ፖስት በያዝነው ዓመት በፈረንጆቹ 2024 ግማሽ የሚሆነውን የአፍሪካ የሀገር ውስጥ ምርትን (GDP) የሚመጣው ከአምስት ሀገሮች እንደሆነ በመግለፅ እነሱም አልጄርያ ፤ ግብፅ ፤ ኢትዮጵያ ፤ ናይጄርያ እና ደቡብ አፍሪካ እንደሆኑ ይናገራል።ሀቅቼክ መረጃ እና ምንጮችን አመሳክሮ ይህ መረጃ እውነት እንደሆነ ማረጋገጥ ችሏል።    ሊንክዓለም አቀፉ የገንዘብ ፈንድ (IMF) በቅርቡ ባወጣው ሪፖርት መሰረት ከአፍሪካ የሀገር ውስጥ ምርት ትልቁን ኢኮኖሚ የሚይዘው ከአልጄርያ ፤ ግብፅ ፤ ኢትዮጵያ ፤ ናይጄርያ እና ደቡብ አፍሪካ የሚገኘው ምርት (GDP) እንደሆነ ገልጿል። 

ሊንክ

ሀገራትየአሜሪካ ዶላር (በቢልዮን) 
ደቡብ አፍሪካ373.233
ግብፅ347.594
አልጄርያ266.780
ናይጄርያ 252.738
ኢትዮጵያ 205.130

የ2024 የሀገራት GDP ሰንጠረዥ

በፈረንጆቹ ሚያዝያ 2024 እንደተለቀቀው የአለም ኢኮኖሚ ሪፖርት ከሆነ ከእነዚህ አምስት ሀገሮች የሚመረተው ምርት የአህጉሪቱን ግማሽ የሚሆነውን ምርት (GDP) እንደሚይዝ ያስቀምጣል። በፈረንጆቹ 2024 ከኤርትራ እና ከምዕራብ ሰሀራ ውጭ የአህጉሪቱ አጠቃላይ GDP 2,819.317 ቢልዮን የአሜሪካን ዶላር ሲሆን እነዚህ አምስት ሀገራቶች ከዚህ ውስጥ 1,445.475 ቢልዮን የአሜሪካን ዶላር የሚሆነውን ይሸፍናሉ።


ሊንክ

አለም አቀፉ የገንዘብ ፈንድ (IMF) ባስቀመጠው ትንተናም የአፍሪካን ኢኮኖሚ በመምራት ዘንድ እነዚህ የአፍሪካ ሀገራቶች ትልቁን ድርሻ እንደሚወስዱ አጽኖት ስጥቶ ገልፆታል። አልጄርያ ፤ ግብፅ ፤ ኢትዮጵያ ፤ ናይጄርያ እና ደቡብ አፍርካን በተለያዩ አለም አቀፍ እና አህጉራዊ ፈተናዎች ውስጥ ሆነው በአህጉሪቱ በሚታዩ የኢኮኖሚ ምህዳር ውስጥ ትልቅ እና ቁልፍ ተዋናዮች በመሆን ጠንካራ እድገትን አሳይተዋል።    

እነዚህን መረጃዎች ስናጠናክር ይህ በX ወይም በቀድሞ መጠሪያው ትዊተር ላይ ምንጭ በመጥቀስ የተጋራው መረጃ ትክክል መሆኑን ሀቅቼክ ማረጋገጥ ችሏል።

         

Exit mobile version