አልጀዚራ ነሃሴ 13 2013 ዓ.ም በፌስቡክ ገፁ ባጋራው ፅሁፍ “ኤርዶጋን በኢትዮጵያ ትግራይ ያለውን ግጭት ለማደራደር ጥያቄ አቅርበዋል” ብሏል።

ልጥፉ በ አርእስት ፅሁፉ “የቱርኩ ፕሬዝዳንት ከኢትዮጵያው ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ጋር ተገናኝተዋል ነገር ግን ምንም አይነት ስምምነት ይፋ አልተደረገም” ይህ የፌስቡክ ልጥፍ ከ 437 በላይ በሆኑ ተጠቃሚዎች ተጋርቷል።

ሀቅቼክ በድረ-ገፁ ውስጥ ያለው ፅሁፉ መርምሯል። በፅሁፉ ውስጥም የቱርኩ ፕሬዝዳንት ረሲፕ ጣይብ ኤርዶጋን በኢትዮጵያና ትግራይ ያለውን ግጭት ለማደራደር ጥያቄ ስለማቅረባቸው የሚገልጽ መረጃ ሰላለመኖሩ አረጋግጧል። ሰለሆነም ሀቅቼክ በፌስቡክ ልጥፉ እና በድህረ ገፁ ባለው ፅሁፍ መካከል ምንም አይነት ግንኙነት እንደሌለ በማረጋገጥ ይህን የፌስቡክ ልጥፍ  አሳሳች አርእስት ብሎታል።

የኢትዮጵያው ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ነሃሴ 13 2013 ዓ.ም በቱርክ አንካራ የአንድ ቀን የስራ ጉብኝት አድርገዋል። በጉብኝታቸውም ከቱርክ አቻቸው  ረሲፕ ጣይብ ኤርዶጋን ጋር በሁለትዮሽ እና በቀጠናው ጉዳይ ላይ ተወያይተዋል። ፕሬዝዳንት ኤርዶጋን በኢትዮጵያ ትግራይ ላለው ግጭት ሰላማዊ መፍትሄን እንደሚደግፉ  መናገራቸው ተዘግቧል።

በተጨማሪም ፕሬዝዳንቱ በኢትዮጵያና ሱዳን ድምበር መካከል ባለው የአልፋሻቅ መሬት ላይ ያለውን የድምበር ግጭት ለማደራደር ፍላጎት እንዳላቸው ተናግረዋል።

የኢትዮጵያውን ጠቅላይ ሚኒስትር በአንካራ የነበራቸውን ጉብኝት አያይዞ አል-አረቢያ እንግሊዝኛ ባሳተመው ጽሁፍ ፕሬዝዳንት ረሲፕ ጣይብ ኤርዶጋን በኢትዮጵያና ትግራይ ታጣቂዎች መካከል ያለውን ግጭት ለማደራደር ጥያቄ አቅርበዋል ሲል አስነብቧል።  

ቀጥሎም አልጀዚራ በፌስቡክ ገጹ ላይ “ኤርዶጋን በኢትዮጵያ ትግራይ ያለውን ግጭት ለማደራደር ጥያቄ አቅርበዋል” የሚል አርዕስት ያለው ጽሁፍ ለጥፏል።   

            ምስል፡ ከድህረ ገፁ ከተገኘ ፅሁፍ

ይሁን እንጂ በድህረ ገፁ ውስጥ ያለው ፅሁፍ ኤርዶጋን በኢትዮጵያ ትግራይ ያለውን ግጭት ለማደራደር ጥያቄ ስለማቅረባቸው ምንም አይናገርም። ፅሁፉ በፌስቡክ ላይ ካለው ልጥፍ ጋር በ ርዕስም ሆነ በይዘት ይለያያል።

በድህረ ገፁ ላይ ያለው ፅሁፍ አርዕስት ኤርዶጋን በኢትዮጵያ ትግራይ ላለው ግጭት ሠላማዊ መፍትሄ እንደሚፈልጉ የሚናገር ሲሆን በአስር ሺዎች ለሚቆጠሩ ሰዎች መፈናቀል እንዲሁም በሚሊየኖች ለሚቆጠሩ ሰዎች መራብ ምክንያት የሆነው ይህ ግጭት በሠላማዊ መንገድ እንዲፈታ ያላቸውን ፍላጎት መናገራቸውን ይነበባል። 

በተጨማሪም ፕሬዝዳንቱ በኢትዮጵያና ሱዳን ድምበር መካከል ያለውን የድምበር ግጭት ለማደራደር ቱርክ ፍላጎት እንዳላት መናገራቸውን ይገልጻል።

 ምስል፡ አሶሽየትድ ፕሬስ

ሰለሆነም በፌስቡክ ልጥፉ ላይ ያለው አርዕስት በድህረ ገፁ ካለው ፅሁፍ ጋር ሀሰተኛ ግንኙነት እንዳለው ሀቅቼክ ስላረጋገጠ የፌስቡክ ልጥፉ ላይ ያለውን መረጃ አሳሳች አርእስት ብሎታል።

Similar Posts