በ5 የካቲት 2013 ዓ.ም Gonder tube/ጎንደር የተባለ (ከ 141,693 በላይ ተከታዮች ያሉት) የፌስቡክ ገፅ የቀድሞው የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝን ምስል በመለጠፍ  ከ CJTN ጋር ባደረገው ቃለ መጠይቅ ወቅት ለኦሮሚያ ብልጽግና ፓርቲ ማስጠንቀቂያ ሰጥቷል በማለት አጋርቷል። ጓደኞቹም መረጃውን እንዲያካፍሉ ጥያቄ አቅርቧል። በአማርኛ የተፃፈው ፅሁፍ “… የኦሮሞ ብልፅግና ያልተረዳው ሀቅ ቢኖር ጀዋርም ሆነ ቄሮ የሚባለው ቡድን ለእኔ ስልጣን መልቀቅ ቅንጣት ሚና አልነበራቸውም እኔ ስልጣኔን ያስረከብሁት ህወሃትን የአማራ ህዝብ መፈናፈኛ ስላሳጣ ነበር የኦሮሞ ብልፅግና ከህወሓት መማር ይኖርበታል ሲሉ ለሲጅቲኤን ተናግረዋል…” ሲል ይነበባል። ሆኖም ሀቅቼክ ጉዳዩን በመመርመር የቀድሞው ጠ / ሚ ኃይለማሪያም የኦሮሚያን ብልጽግና ፓርቲን እንዳላስጠነቀቁ እንዲሁም በቅርቡ ከ ሲጂቲኤን (CJTN) ጋር ቃለ ምልልስ እንዳላደረጉ አረጋግጧል። ሰለዚህ መረጃውን ሀሰት በማለት በይኖታል።

 

የደርግ ስርዓት ካለቀበት 1983 ዓ.ም ጀምሮ የኢህአዲግ ጥምረት / ፓርቲ ለሁለት አስርት ዓመታት ኢትዮጵያን ገዝቷል። ህወሃት በጥምረቱ ውስጥ እስከ 2010 ዓ.ም ድረስ የበላይነት የነበረው ሲሆን የቀድሞው ጠ/ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ከሞቱ በኋላ የኢኮኖሚ ማሽቆልቆል እና ሕዝባዊ አመጾች በመላ አገሪቱ ተከስቶ ነበር። ከመንግስት ተቃዋሚዎች መካከል የብዙሃን የተቃውሞ ሰልፎች መሐንዲስ  የነበረው አንዱ መሪ ጃዋር መሃመድ በኦሮሚያ ቄሮ የሚባለውን የኦሮሞ ወጣቶች አደረጃጀት በመመስረት መንግስት በብዙ ዘርፎች ማሻሻያዎችን እንዲያደርግ ተጽዕኖ አርጓል። እነዚህ እንቅስቃሴዎች የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ በሚያዚያ 2010 ዓ.ም ስልጣናቸውን እንዲለቁና በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ አሊ (ፒኤችዲ) እንዲተኩ አስተዋትጾ አርጓል። 

በ 2012 ዓ.ም ኢህአዴግ አንድ ፓርቲ በመሆን ስሙን ወደ ብልጽግና ፓርቲ ቀይሯል። ህወሃትም ፓርቲውን ለመቀላቀል የቀረበትንን ጥሪ ውድቅ በማድረግ ወደ ትግራይ ክልል ተመልሷል። ከዛም በኋላ 25 ጥቅምት 2013 ዓ.ም በሰሜን እዝ ላይ በተደረገው ጥቃት በሕወሃት በሚመራው የትግራይ ክልል ኃይል እና በፌዴራል መንግሥት በሚመራው ኃይል መካከል የትጥቅ ትግል ተካሂዷል። በፌዴራሉ መንግስት የሚመራው ኃይል የህወሃት ኃይል እና ዋና አመራሩን አፍርሷል ቢባልም በትግራይ ክልል ውስጥ ያለው አለመረጋጋት ቀጥሏል።

የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር ለኦሮሚያ ብልጽግና ፓርቲ አስጠነቀቀ በማለት በፌስቡክ ላይ የተለቀቀው ልጥፍ በሰፊው እየተሰራጨ ሲሆን በሌሎች ተጠቃሚዎች ከ147 ጊዜ በላይ ተጋርቷል። ሆኖም የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር በቅርቡ ከሲጄቲኤን ጋር ቃለ ምልልስ አለማረጋቸውን እና ለኦሮሚያ ብልጽግና ፓርቲ ምንም አይነት ማስጠንቀቂያ በቪዲዮም ሆነ የጽሑፍ ቃለ ምልልስ እንዳልሰጡ የመገናኛ ብዙሃኑ ሁሉም ገፆች ላይ በተደረገ ምርመራ ለማወቅ ተችሏል። በእርግጥ በፌደራል መንግስቱ እና በህወሃት ኃይሎች መካከል እየተካሄደ ያለውን የትጥቅ ግጭት አስመልክቶ በውጭ ፖሊሲ ላይ የአስተያየት መጣጥፍ ፅፈዋል ፡፡

ስለሆነም ሀቅቼክ ጉዳዩን መርምሮ የቀድሞው የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ኃይለማሪያም ደሳለኝ የኦሮሚያን ብልጽግና ፓርቲን እንዳላስጠነቀቁ እና ልጥፉን ለመደገፍ የተጠቀሙት ማጣቀሻ ትክክለኛ አለመሆኑን ሰላገኘ መረጃው ሀሰት መሆኑን አረጋግጧል ፡፡

አጣሪ፡ ሓጎስ ገብረአምላኽ

ተርጓሚ፡ ርሆቦት አያሌው

አርታኢ፡ ብሩክ ነጋሽ

ይህ ፅሑፍ በአዲስ ዘይቤ የምርምርና ተቋም ግንባታ ቢሮ (Addis Zeybe Research & Development Department) በሚመራው ፤ ሀቅቼክ የተዘጋጀ ሲሆን ሀቅቼክ በአምስት ቋንቋዎች (አማርኛ፣ ኦሮምኛ፣ ትግርኛ፣ ሶማልኛ እና እንግሊዘኛ ቋንቋዎች) እየተዘጋጀ የሚቀርብ የተለያዩ መረጃዎችን ሀቅነት የሚመረምር የአዲስ ዘይቤ መርሀ ግብር ነው። 

Similar Posts