በ16 ጥር 2013 ዓ.ም ታጅዲን አህማዲ(Taajudin Ahamadi) የተባለ (ከ 3,900 በላይ ጓደኞቹ ያሉት) የፌስቡክ ተጠቃሚ ከዚህ በታች ያለውን ምስል የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ (ዶ/ር) በጠና ታመው በሆስፒታል ውስጥ ህክምና እየተደረገላቸው ነው በማለት አጋርቶ ነበር። ልጥፉ የወጣው የጠቅላይ ሚኒስትሩን ከሚዲያ መጥፋት ተከትሎ ስለደህንነቱ ጥርጣሬዎች እና የተለያዩ ግምታዊ አስተያየቶች እየተሰራጩ ባለበት ወቅት ነበር። ልጥፉ በተለያዩ ተጠቃሚዎች ሲሰራጭ ተስተውሏል። ሆኖም ሀቅቼክ ጉዳዩን መርምሮ ምስሉ ጠ/ሚ አብይ አሕመድ መታመማቸውን እና በሆስፒታል ውስጥ እየታከሙ መሆኑን የማያሳይ እና ቅንብር መሆኑን አረጋግጧል።

 

ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ የጠ/ሚ ዐብይ አህመድ (ዶ/ር) ከሚዲያ መጥፋት ተከትሎ ስለደህንነቱ ጥርጣሬዎች እና የተለያዩ ግምታዊ አስተያየቶች እየተሰራጩ ይገኛል። አንዳንዶች ጠቅላይ ሚኒስትሩ በጠና መታመማቸውን ሌሎች ደግሞ ሞተዋል በማለት ገምተዋል። ነገር ግን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት በጠቅላይ ሚኒስትሩ ደህንነት ዙሪያ የሚነሱ ግምቶች ሐሰት መሆናቸውን አስታውቋል።  እነዚህ ያልተረጋገጡ ግምቶች እየተሰራጩ ባሉበት መካከል በ20 ጥር 2013 ዓ.ም ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለተጎዱ ወታደሮች እና ሲቪሎች የሰው ሰራሽ አካላት ማምረቻን ሲጎበኙ ታይተዋል

ሆኖም ሪቨርስ ኢሜጅ የተባለ የምስል ማጣሪያ እንደሚያሳየው ምስሉ ለመጀመሪያ ጊዜ የታተመው ጎፈንድሚ በተባለ የበይነ መረብ የገንዘብ ማሰባሰቢያ ሲሆን ቢድሃን ታፓ የተባለ ሰው በደረሰበት የልብ ምት ማቋረጥ (cardiac arrest) ምክንያት ሲረዳበት በነበረው ጆን ሆፕኪንስ ሆስፒታል መሞቱን ተከትሎ የቢድሃን ታፓ ሚስት ፕሪስኪላ ራይን ለመርዳት ምስሉን በመጠቀም ገንዘብ ለመሰብሰብ በድረ ገፁ ላይ ተለጥፏል። 

የተቀናበረው ምስል

የመጀመሪያው ምስል

ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ በጠ/ሚ ዐብይ አሕመድ ደህናነት እና የጤና ሁኔታ ላይ የተለያዩ ጥያቄዎች እና መላምቶች ሲነሱ ይስተዋላል። ሆኖም ሀቅቼክ ልጥፉን ከመረመረ በኋላ ምስሉ ጠቅላይ ሚኒስትሩ መታመማቸውን እንዲሁም በሆስፒታል ውስጥ በመታከም ላይ መሆናቸውን የማያሳይ እና ቅንብር መሆኑን አረጋግጧል።

 

አጣሪ፡ ሓጎስ ገብረአምላኽ

 

ተርጓሚ፡ ርሆቦት አያሌው

አርታኢ፡ ብሩክ ነጋሽ

ይህ ፅሑፍ በአዲስ ዘይቤ የምርምርና ተቋም ግንባታ ቢሮ (Addis Zeybe Research & Development Department) በሚመራው ፤ ሀቅቼክ የተዘጋጀ ሲሆን ሀቅቼክ በአምስት ቋንቋዎች (አማርኛ፣ ኦሮምኛ፣ ትግርኛ፣ ሶማልኛ እና እንግሊዘኛ ቋንቋዎች) እየተዘጋጀ የሚቀርብ የተለያዩ መረጃዎችን ሀቅነት የሚመረምር የአዲስ ዘይቤ መርሀ ግብር ነው። 

Similar Posts