በ21 ታህሳስ 2013 ዓ.ም Mahder Kiya ማህደር ቅያ የተባለ (ከ10,000 በላይ ተከታዮች ያሉት) አንድ የፌስቡክ ተጠቃሚ ከዚህ በታች ያለውን የአንድ ኦራል የጭነት መኪና እና አንድ ወታደር ምስል በህወሃት የሚመራው ኃይል ከአድዋ ወደ ሀውዜን ሲጓዝ  አንድ የፌደራል መከላከያ ሰራዊት ብርጌድ ደምሷል ከሚል ፅሁፍ ጋር አጋርቷል። በትግርኛ የተፃፈው ፅሁፍ “…የ 33 ኛው ክፍለ ጦር ከአድዋ ወደ ሃውዜን በእዳጋ አርቢ በኩል ሲጓዝ በነበረ ሀይል ተመቶ ሙሉ በሙሉ አድብቶ 144 ወታደሮች እና ሁሉም የጦር መኮንኖች ተያዙ…” ሲል ይነበባል። ሆኖም ሀቅቼክ ጉዳዩን መርምሮ ምስሉ ትግራይ ውስጥ በተፈጠረው ግጭት አራተኛውን የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊትን ያጠፋውን በህወሃት የሚመራ ሃይል የማያሳይ በመሆኑ እና ምንም ግንኙነት እንደሌለው በማረጋገጡ መረጃውን ሀሰት ሲል ፈርጆታል።

ከ28 ጥቅምት 2013 ዓ.ም ጀምሮ በፌዴራል መንግስት እና በህወሃት በሚመራው የትግራይ ልዩ የፖሊስ ኃይል እና ሚሊሻ መካከል በትግራይ ክልል ውስጥ ግጭት መከሰቱ እውነት ነው። የፌዴራል መንግሥት ጦርነቱ መጠናቀቁን እና ቀጣዩ እርምጃ የህውሃት አመራሮችን አድኖ ማግኘት መሆኑን ቢናገርም፤ በፌዴራልና በክልል ኃይሎች መካከል ያለው ጦርነት አሁንም እንደቀጠለ ያልተረጋገጡ መረጃዎች እየወጡ ይገኛሉ።

ሆኖም ሪቨርስ ኢሜጅ የተባለ የምስል ማጣሪያ እንደሚያመለክተው ምስሉ የአራተኛውን ብርጌድ ወታደሮች እና የጦር መሳሪያዎች መያዛቸውን አያሳይም። ምስሉ ለመጀመሪያ ጊዜ ታትሞ የወጣው ህውሓት ሀወልቲ በተባለ የፌስቡክ ገጽ 1 ህዳር 2013 ዓ.ም ሲሆን ትግራይ ከቀደሙት ጊዜያት በተለየ ዘመናዊ የጦር መሣሪያ የታጠቀች መሆኑንና በትግራይ ላይ ጦርነት ለማካሄድ በሚደፍሩ ጠላቶች ላይ ድል አድራጊ ይሆናል ከሚል ፁሁፍ ጋር ነበር በወቅቱ የተለቀቀው። 

ብመሆኑም በፌዴራል እና በትግራይ ክልል ኃይሎች መካከል የተደረገው ጦርነት አሁንም እንደቀጠለ ያልተረጋገጡ ዘገባዎች ቢኖሩም ሀቅቼክ የፌስቡክ መረጃውን መርምሮ ምስሉ በህወሃት የሚመራው ኃይል አራተኛውን የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊትን መያዙን የማያሳይ ስለሆነ ጥቅም ላይ የዋለው ምስል ሀሰት መሆኑን አርጋግጧል።

አጣሪ፡ ሓጎስ ገብረአምላኽ

ተርጓሚ፡ ርሆቦት አያሌው

አርታኢ፡ ብሩክ ነጋሽ

ይህ ፅሑፍ በአዲስ ዘይቤ የምርምርና ተቋም ግንባታ ቢሮ (Addis Zeybe Research & Development Department) በሚመራው ፤ ሀቅቼክ የተዘጋጀ ሲሆን ሀቅቼክ በአምስት ቋንቋዎች (አማርኛ፣ ኦሮምኛ፣ ትግርኛ፣ ሶማልኛ እና እንግሊዘኛ ቋንቋዎች) እየተዘጋጀ የሚቀርብ የተለያዩ መረጃዎችን ሀቅነት የሚመረምር የአዲስ ዘይቤ መርሀ ግብር ነው። 

Similar Posts