በዩቱዩብ ፣ በድህረ ገጽ እንዲሁም ከ484,227 በላይ ተከታይ ባለው በፌስቡክ ገጽ ላይ  “ቴዲ አፍሮ ሰራዊቱን ስርፕራይዝ አደረገ” በማለት አንድ ተንቀሳቃሽ ምስልን አጋርቷል። 

ይህ ጽሁፍ ለንባብ እስከበቃበት ጊዜ ድረስ ተንቀሳቃሽ ምስሉ በድህረ ገጹ ላይ ከ20,900 ጊዜ በላይ የታየ ሲሆን፣ የፌስቡክ ልጥፉ ደግሞ 1,700 ያህል ሪአክሽን አግኝቶ ከ60 ጊዜ በላይ ተጋርቷል። ከድህረ ገጹ እና ከፌስቡክ ልጥፉ አስቀድሞ ተንቀሳቃሽ ምስሉ የተለቀቀው በመስከረም 6 ፣ 2014 ዓ.ም በዩቱዩብ ቻናሉ ላይ ሲሆን ከ1,120 በላይ ዕይታም አግኝቷል። 

ይሁን እንጂ ፣ የፌስቡክ ልጥፉ አርቲስት ቴዎድሮስ ካሳሁን በጦላይ ማሰልጠኛ ማዕከል ተገኝቶ ወታድሮችን ሲያዝናና ስለማያሳይ ልጥፉ ሀሰት ነው።

 

ከህዳር 2012 ዓ.ም ጀምሮ የትግራይ ህዝብ ነጻ አውጪ ግምባር(ትህነግ) ሃይሎች በሰሜኑ የኢትዮጵያ ክፍል ከኢትዮጵያ የፌደራሉ መንግስት ጋር ጦርነት ላይ ናቸው። የተለያዩ የሃገር ውስጥ ሚዲያዎች በኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት የስልጠና ካምፖች ውስጥ በጣም ብዙ አዳዲስ ምልምል ሰልጣኝ ወጣቶች እየተቀላቀሉ እንደሆነ ዘግበዋል። ይህንንም በማስመልከት አርቲስቶች እንዲሁም ትላልቅ የመንግስት ባለስልጣናትን ጨምሮ ለአዳዲስ ምልምል እና ተመራቂ ወታደሮች ካምፖቻቸው ድረስ እንዲሁም የጦር ግምባሮች ድረስ በመሄድ ጎብኝተው አነቃቅተው እና አበረታተው ተመልሰዋል ተብሎ ሲዘገብ ሰንብቷል።

ቴዎድሮስ ካሳሁን ወይም በቅጽል ስሙ ቴዲ አፍሮ በኢትዮጵያ እና ኤርትራ ብዙ አድናቂዎች ያሉት ሙዚቀኛ ሲሆን “ኢትዮጵያ” የሚለው 5ተኛው አልበሙ በግንቦት 12 ፣ 2009 ዓ.ም በአለም የቢልቦርድ ሰንጠረዥን ተቆጣጥሮ ነበር። 

ይህን ተከትሎ የተሰራጨው ተንቀሳቃሽ ምስል የፊትለፊት ምስል  የተቀነባባረ እንደሆነ ለማውቅ ተችሏል። ምስሉ የድምጻዊውን ፊት በተሰበሰቡ የሰራዊት አባላቶች መካከል በማቀናበር የተሰራ ሲሆን ከዚያም ባላፈ ግን የተንቀሳቃሽ ምስሉ ይዘት በውስጡ የቴዎድሮስ ካሳሁን እና የሰራዊቱ የተለያዩ ምስሎች ለየብቻ የሚያሳይ ነው።  

ከዚህም በተጨማሪ የድምጻዊው ማናጀር ከሆኑትን አቶ ጌታቸው ማንጉዳይ በስልክ ባደረግነው ቆይታ መረጃው ፍጹም ሀሰት እንደሆነ እና አርቲስት ቴዎድሮስ ካሳሁንም በጦላይ ማሰልጠኛ እንዳልተገኘ አስረድተውናል።    

ስለዚህ በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ አርቲስት ቴዎድሮስ ካሳሁን በጦላይ ማሰልጠኛ ተገኝቶ ሰራዊቱን አዝናና የሚለው መረጃ ሀሰት መሆኑ ትርጋግጧል  

              

 

Similar Posts